0 0
Read Time:39 Second

በሆሮ ጉድሩ ዞን አቢ ደንጎሮ ወረዳ እስካሁን 10 የሚሆኑ የገጠር ቀበሌዎች በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ መያዛቸውን ተከትሎ መንገድ ከተዘጋ ስድስት ወር አልፏል።

የሽብር ቡድኑ በሚያደርገው ዘር ተኮር ደመ ነፍሳዊ እንቅስቃሴ የተነሳ በርካቶች በአማራዊ ማንነታቸው ብቻ ተገድለዋል፣ ተዘርፈዋል፤ ቤታቸው ተቃጥሏል፤ ባልና ሚስት፣ልጅ እና እናት ጎሳቸው ተቆጥሮ እንዲለያዩ ተደርጓል።

ከዚህም ባሻገር አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶች ወድመዋል፤ አባቶች ተገድለዋል፣ ተሳደዋል፤ ተዘርፈዋል፤ አብያተ ክርስቲያናት የወታደር ማሰልጠኛ እስከመሆን ደርሰዋል።

ከሁሉም በላይ ሽህዎች ተፈናቅለው ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል፤ አንዳች የሰብአዊ እርዳታ የሚያቀርብላቸው አካል እንዳልተገኘ እየተናገሩ ነው።

አሁን ላይ የፌደራል ፖሊስ የገባ ቢሆንም ተቋማት ግብአት ስለሌላቸው መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በተለይ የጤና ተቋማት የመድሃኒት አቅርቦት ስለሌላቸው ክፉኛ መቸገራቸውን ገልጸዋል።

የሽብር ቡድኑና መሰሎቹ ምንም ዓይነት የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት በተለይም ሸቀጣ ሸቀጥ ለአማራው እንዳይሸጥ ከልክለዋል ይላሉ።

በመሆኑም ኑሮአችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ በመምጣቱ የፌደራል መንግስት አንዳች መፍትሄ ያመጣ ዘንድ እንማጸናለን ብለዋል።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator