0 0
Read Time:42 Second

በተንታ ወረዳ የፋኖ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በቀን 16/07/2014ዓ.ም ከጧቱ 12:20 ላይ በስልጠና ቦታ እያሉ በወረዳው ፖሊስ መምሪያ ሀላፊና በሚኒሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አዛዥነት እስሩ እንደተፈፀመባቸው ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የታሰሩትም በቁጥር 12 ሲሆኑ ስማቸውም:_

1.ታድሷል ታምሬ/አሰልጣኝ፣
2.ምሳየ ጌታነህ/አሰልጣኝ፣
3.ብርሀነ ገብረ መስቀል፣
4.ቴዲ ብርሀኑ፣
5.ሙሀመድ ካሳ፣
6.ፈርሀት ኑርየ፣
7.አዲሱ ተፈራ፣
8.አብዱ ሙሀመድ፣
9.ሙሀመድ በሽር፣
10.መኮንን ዋስየ እና ሌሎችም ይገኙበታል።

ከዚህ በፊት ፋኖ አትሰለጥኑም በማለት በወረዳው መታሰራቸው ይታወሳል።

ይህ ድርጊት ሲፈፀም ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

አሁንም እስር ቤት የሚገኙ ሲሆን “ከእስር የምንለቃችሁ ከዚህ በኋላ ፋኖ አንሰለጥንም ብላችሁ ከፈረማችሁ ብቻ ነው” ተብለዋል።

ለቀረበላቸው ጥያቄም የታሰሩት ፋኖዎች “አንፈርምም፣ እንሰለጥናልም” የሞል ምላሽ ሰጥተዋል።

የወረዳው ፖሊስ ሀላፊ እንግዳውስ “ከእስር አትፈቱም እርምጃም ይወሰድባችኋል” በማለት እየዛቱባቸው መሆኑና በእስር ላይ እንደሚገኙ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
መረጃው የደቡብ ወሎ ፋኖ አስተባባሪ የአቶ ኤርሚያስ አያሌው ነው።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator