0 0
Read Time:41 Second

መዋቅራዊ ድጋፍ ያለው አሸባሪው ኦነግ ሸኔ እና የዘር ማጥፋት ተባባሪዎቹ
በምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ አማራዎችን በተኩስ እሩምታ ጨፈጨፉ።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ አልጌ ቀበሌ መጋቢት 8/2014 ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በአማራዎች ላይ ማንነት ተኮር ጥቃት እየተፈጸመ ነው።

አንድ ካራንቡላ ቤት ብቻ የነበሩ 7 ወጣቶችን በጥይት ደብድበው ከመግደል አልፈው ቤት ለቤት በመዞር ማንነት ተኮር ግድያ መፈጸማቸው ተገልጧል።

መጋቢት 8/2014 ከምሽቱ 2 ሰዓት የጀመረው ጥቃት ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ድረስ እንዳልቆመና የደረሰ አንድም የጸጥታ አካል አለመኖሩን ተደብቀው የተረፉ ነዋሪዎች ለአሚማ ተናግረዋል።

ታቅዶበት ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት ለጊዜው የደረሰንን መረጃ ብንመለከት ከተገደሉት 8 ሰዎች መካከል 6 አማራዎች ሲሆኑ 2ቱ የወላይታ ተወላጆች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

ከ6 በላይ አማራዎች የቆሰሉ ስለመሆኑና ወደ ህክምና ለማድረስ እና የተገደሉትን አስከሬን ለማንሳት ከተደወለላቸው የጸጥታ አካላት መካከል አንዱም እንኳ ለመድረስ አለመቻሉን ለማወቅ ተችሏል።

የፌደራል ፖሊስ የመረጃ ክፍል “ነገ ደውሉ” የሚል አሳዛኝና አሳፋሪ ምላሽ ሰጥተዋል።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator