0 0
Read Time:48 Second

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከማሼ ዞን ሚዥጋ ወረዳ አንገር ሜጢ ቀበሌ ዓመቱን ሁሉ የደከሙበትን አዝመራ ምርት በመሰብሰብ ላይ የነበሩ 26 አማራዎች ተገድለዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ታህሳስ 13 ቀን 2014 ሲሆን ስርዓተ ቀብራቸው በአካባቢው ባሉ ጉምዞች መፈጸሙ ተገልጧል።

የአካባቢው ምንጮች ለአሚማ እንደገለጹት ከተገደሉት ሰዎች መካከል:_

1)ቢሻው ይርሳው፣
2) ምትኩ ቢሻው፣
3) በልስቲ ይርሳው፣
4) ተዋቸው አስማረ፣
5) ሸጋው ጫኔ፣
6) ፈንታሁን ቢሻው፣
7) አስቴር፣
8/ ትብለጥ እና
9) ዘመን ገደፋዬ የተባሉ አማራዎች ይገኙበታል።

በተመሳሳይ 3 ሴቶች በሽብር ቡድኑ ታግተው መወሰዳቸው ተገልጧል፤ አንድ ሰው ደግሞ አምልጦ ወደ ነቀምት ማለፉ ተሰምቷል።

በተመሳሳይ በወሪንቃ ቀበሌ ታህሳስ 15 ቀን 2014 አቶ ጌታቸው ሀሰን የተባሉ ርሃብ የጠናባቸው ተፈናቃይ አባት ወደ አዝመራቸው ሲሄዱ ታርደዋል ተብሏል።

አስከሬን ፍለጋ ታህሳስ 17 ቀን 2014 ፍለጋ ሲሄዱ ደግሞ አቶ ሸጋ ሀሰን የተባለ ሰው ደግሞ በወሪንቃ ቀበሌ ዳልቻ አካባቢ ሲደርስ መቁሰሉ ተሰምቷል።

ይህ ሁሉ ሲሆን ወረዳ ላይ ያለው መከላከያና ልዩ ኃይል፣ አዋሳኝ በሆነው ሳሲጋ ወረዳ በሬዳ ዙሪያ ያለው የመከላከያ ኃይል እነዚህን ኃይሎች ለማጥፋት አለመንቀሳቀሱ ብዙዎችን ያሳዘነ መሆኑ ምንጮች ለአሚማ ተናግረዋል።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator