0 0
Read Time:45 Second

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አሞራ ቤት ቀበሌ አውራ ጎዳና አካባቢ የኦሮሚያ የጸጥታ አካላት እንቅስቃሴ እና የክምችት መጠን በተለይ ከመጋቢት 20/2014 ጀምሮ በአሳሳቢ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑ ተገልጧል።

የአውራ ጎዳና እና አካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ከመጋቢት 20/2014 ጀምሮ የገባው መከላከያ መጋቢት 22/2014 መነሳቱን አውስተዋል።

መከላከያ ከአውራ ጎዳና መውጣቱን ተከትሎ የኦሮሚያ ጥምር ኃይል የቡድን መሳሪያ ይዞ ከመተሃራ ወደ ቦሰት አቅጣጫ ከተማዋን ከ6 ጊዜ በላይ ዞሯል፤ ለጠባጫሪነትና ለጥናት ሊሆን እንደሚችልም ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባን መስመር ጨምሮ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኦሮሚያ የጸጥታ ኃይል በመመጓጓዝ በወረንጭቲ እና በመተሃራ እየሰፈረ መሆኑን የገለጹት ነዋሪዎች በአማራ ክልል በኩል ግን መዘናጋት እየተስተዋለ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በኦሮሚያ በኩል እየተደረገ ያለው ኃይለኛ የሆነ ዝግጅት ነገ ከነገ ወዲያ በተዘናጋ የአማራ የጸጥታ አካል እና ህዝብ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል እንዳይፈጸም ከፍተኛ ስጋት ስላለን በአስቸኳይ ይህ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አካሄድ ሊወገዝና ሊስተካከል ይገባዋል ሲሉ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አሞራ ቤት ቀበሌ የአውራ ጎዳና ነዋሪዎች ጥሪ አድርገዋል።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator