0 0
Read Time:47 Second

ከምስራቅ ወለጋ የተፈናቀሉ አማራዎች!

ከምስራቅ ወለጋ ዞን ሌቃ ዱለቻ ወረዳ ተፈናቅለው በገተማ እና ከዋዩጡቃ ወረዳ ተፈናቅለው በጉቴ ተጠልለው የሚገኙ በትንሹ ከአስር ሽህ በላይ የሚሆኑ አማራዎች ስላሉበት ሁኔታ አሚማ ለማነጋገር ሞክሯል።

ለዘመናት ከሚኖሩበት ቀዬ እንዲፈናቀሉ የተደረጉ አማራዎች አሁን ላይ “በመጠለያ ሳይሆን በመጣያ ውስጥ ነው ያለን፤ የደህንነት ስጋት አለብን፤ ከተጠለልንበት በቦንብ ለማጥቃት ሁለት ሶስት ጊዜ ተሞክሯል!” ይላሉ።

አሁን ላይ በመጠለያ ውስጥ ያሉ ብዛታቸውም በጉቴ ከተማ 5,650 አባዎራ እና እማዎራዎች፣ ከእነ ቤተሰቡ ከ10,000 በላይ ይሆናሉ፤ በገተማ ደግሞ ከ1,500 በላይ አባዎራ እና እማዎራዎች፣ ከእነ ቤተሰቡ ከ2,500 በላይ እንደሚሆኑ ተገልጧል።

በደህንነት ስጋት ምክንያትም በመቶዎች የሚቆጠሩ አባዎራ እና እማዎራዎች ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተበትነዋል።

እነዚህ ከምስራቅ ወለጋ ዞን ሌቃ ዱለቻ እና ዋዩጡቃ የተፈናቀሉ አማራዎች እንደሚሉት በጥቅምት 16 ቀን 2014
ከተፈጸመው ግድያና በአስር ሽህዎች መፈናቀል በተጨማሪ በአሸባሪዎች እንቅስቃሴ ሶስት መስጊዶች እና አንድ ቤተ ክርስቲያን እንዲወድም መደረጉን አውስተዋል።

በመጨረሻም በቂ ሰብአዊ እርዳታ እየተደረገልን አይደለም የሚሉት ተጎጅዎቹ በቂ እርዳታ እየደረሳቸው እንዳልሆነ በመግለጽ መንግስት፣ ሀገር ወዳድ የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲደርሱላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator