0 0
Read Time:53 Second

የመተከል አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ በጃዊ ከተማ እስር እና ወከባ እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተገለፀ።

የመተከል አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ በጃዊ ከተማ ጥቃት እየደረሰብኝ ነው ሲል ገልጿል።

የመተከል አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ደመላሽ አንድነው ለንሥር ብሮድካስት እንደገለፁት በወረዳው አስተዳደር በኩል የመተከል አስተዳደር ኮሚቴ እና የቦርድ አባል የሆኑትን የማሰር እና ስም የማጠልሸት ተግባር የተጀመረ ቢሆንም ይህን እኩይ ተግባር በመቋቋም መተከልን ወደ አማራ ጎጃም ግዛት ለማስመለስ የሚያስችል ተግባራትን እየፈፀሙ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

ሆኖም ይላሉ ሰብሳቢው የአዊ ዞን አስተዳደር ከቤኒሻጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት በሚቀበሉት የአማራነት አፍራሽ ተልዕኮ ምክንያት የመተከል አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴን በጠላትነት ፈርጀው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ብለዋል።

በትናትነው ዕለትም የማንነት ኮሚቴ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ እንዳለው አዲስን ከስራ ገበታቸው ላይ እያሉ ፖሊስ እና ሚሊሻ በመላክ ያሰራቸው ሲሆን ሌሎችንም ኮሚቴዎች በተመሳሳይ ለማሰር ማደኛ አውጥተው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በኮሚቴዎች ላይ የሚደርሰው እስርና አደን መተከልን ወደ ጎጃም ነባር ግዛትነት ለመመለስ የሚደረገውን ትግል እንቅፋት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን መላው የአማራ ህዝብ ሊረዳ ይገባል ብለዋል።

አክለውም የአማራ ህዝብ የመተከል ዕርስትን እንደ ወልቃይት፣ ራያ እና ደራ ተመለክቶ ትግሉን ከጎናችን ሆኖ እንዲመራ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ንስር ብሮድካስት እንደዘገበው።

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ

About Post Author

Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %

By Admin

Amhara elites must be militant democrat to stop anti democratic fascism act on our people by those extremist nationalists(TPLF ,OLF), and also name covered prosperity,EPRDF. ትንሳኤ አማራ በልጆቹ ትግል እውን ይሆናል።

Translator